ለ18ኛ ጊዜ የሚከበረው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን “ብዝኃነትና እኩልነት ለሀገራዊ አንድነት“ በሚል መሪ ቃል ህዳር 28 ቀን 2016 ዓ.ም. በኢምባሲው ጽ/ቤት ተከበሯል፡፡

በአከባበር ስነ-ስርዓቱ ላይ በእስራኤል ክቡር የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ተስፋዬ ይታይህ ባስተላለፉት መልዕክት የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በአገራችን ብዝኃነትን እና ህብረ- ብሔራዊነት በህገ መንግስት የፀናበት፣ በእኩልነት፣ በወንድማማችነት እና በመቻቻል አገረ-መንግስት የሚገነባበት የአንድነታችን ምልክት የሆነ ዕለት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በዓለም ላይ የፌዴራል ስርዓት የሚከተሉ አገሮችንና ተሞክሯቸውን በማንሳት የፌዴራሊዝምን ፅንሰ ሃሳብ አብራርተዋል፡፡ ከዚህ አኳያ አገራችን የምትከተለው የፌዴራሊዝም ስርዓት ለብዝኃነት እና ህብረ-ብሔራዊ አንድነት መተግበር ትክክለኛ የመንግስታችን አወቃቀር ሥርዓት መሆኑን ገልጸዋል፡፡በስነ-ስርዓቱ ላይ የሚሲዮኑ ሰራተኞች የተገኙ ሲሆን የዳቦ ቆረሳ እና ዕለቱን የሚያደምቅ ሻማ በማብራት ስነ-ስርዓት በማከናወን ተከብሯል፡፡

Disclaimer: The official text of the Embassy Website is the English language version. Any discrepancies or differences created in translations are not binding and have no legal effect for compliance or enforcement purposes.

X
Twitter
Facebook
YouTube
Instagram